LatestNews

የአፈ-ጉባዔዎች የምክክር መድረክ በላሊበላ ይካሄዳል

ፌዴራል እና የክልል አፈ-ጉባዔዎች የምክክር መድረክ ከነገ ጀምሮ በላሊበላ ከተማ ይካሄዳል፡፡

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሠ ጫፎ እና ምክትል አፈ-ጉባዔ ሽታዬ ምናለ ላሊበላ ገብተዋል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አደም ፋራህ እና ምክትል አፈ-ጉባዔ ዕፀገነት መንግስቱ እንዲሁም የክልል አፈ-ጉባዔዎች ላሊበላ ከተማ ሲደርሱ አቀባበል ተደረጎላቸው፡፡

የላሊበላ ከተማ ከንቲባ አቶ ይልማ መርቅ ለአፈ- ጉባዔዎቹ ልኡካን አቀባበል አድርገውላቸዋል።

አፈ-ጉባዔዎቹ ከአቀባበል ሥነ-ሥርዓቱ በኋላ ከሌሎች የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናትን ጎብኝተዋል፡፡

በዚሁ በላሊበላ ከተማ የፌዴራል እና የክልል አፈ-ጉባዔዎች የምክክር መድረክ ከነገ ጀምሮ እንደሚካሄድ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።