EthiopiaNews

በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦች

የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ በነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ዙሪያ ሕገ-ወጥ ድርጊት የፈጸሙ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ 658 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናገሩ።

ሚኒስትሩ ይሄን ያሉት የፌዴራልና የክልል ተቋማትን ያካተተና የነዳጅ ስርጭቱን 24 ሰአታት የሚከታተል የሁኔታዎች ልዩ የመከታተያ ክፍል መቋቋሙን ይፋ ባደረጉበት ወቅት ላይ ነው።

ሚኒስትሩ ጨምረውም ከ720 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ተይዞ ለመንግሥት ገቢ ሆኗል ብለዋል።

መረጃው ከንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የተገኘ ነው።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews