InternationalNews

ኢራን እና እስራኤል

የኢራኑ ሀይማኖታዊ መሪ አያቶላ አሊ ሃማኒ የሃማስ ከፍተኛ መሪ የሆኑት ኢስማኤል ሃኒዬ ቴህራን መገደላቸውን ተከትሎ እስራኤል ላይ የአጸፋ እርምጃ እንዲወሰድ ማዘዛቸው ተሰምቷል።
ሃሚኒ ትዕዛዙን ያስተላለፉት የኢራንን መንፈሳዊ ብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ከጠሩ በኋላ ነው፡፡

ሟቹ የሃማስ መሪ ኢስማኤል ሃኒዬ ቴህራን ተገኝተው የነበሩት አዲስ በተሾሙት የኢራን ፕሬዚዳንት መሱድ ፔዚሽኪያን በዓለ ሲመት ላይ ለመታደም እንደነበር ገልፆ የዘገበው ኒው ዮርክ ታይምስ ነው፡፡