EthiopiaNews

የጋምቤላ የአጀንዳ ልየታ የምክክር መድረክ

በጋምቤላ ክልል ከሀምሌ 22 እስከ ሀምሌ 28/2016 ዓ.ም ሲካሄድ የነበረው የአጀንዳ ልየታ የምክክር መድረክ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

ይህንኑ ተከትሎም በአጠቃላይ 495 የህብረተሰብ ክፍል ወኪሎች የለዩዋቸውን አጀንዳዎች የምክክሩ ባለድርሻ አካላት አደራጅተው ለኮሚሽኑ ማስረከባቸው ነው የተገለጸው፡፡ ከዚህ ባሻገር 115 የሚሆኑ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትና ማህበራት፣ 53 የመንግስት ተቋማትና 30 የፖለቲካ ፖርቲ ተወካዮች እንዲሁም 135 ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተሳታፊዎች ሆነውበታል ተብሏል፡፡