EthiopiaNews

ሃሰተኛ  መድኃኒቶች

በአፍሪካ በታማሚዎች ከሚወሰዱ መድኃኒቶች አንድ አምስተኛው ወይም 20 በመቶው ትክክለኛ ያልሆኑ ወይም ከደረጃ በታች መሆናቸውን አንድ ጥናት አመልክቷል፡፡

በባህርዳር ዩንቨርሲቲ የተጠናውን ጥናት ዋቢ አድርጎ ዘጋርዲያን እንደዘገበው ናሙና ከተወሰዱ 7 ሺ 508 መድሃኒቶች 1 ሺ 639 የሚሆኑት ዝቅተኛ የጥራት ደረጃን የማያሟሉ ወይም ሃሰተኛ ሆነው መገኘታቸው ተረጋግጧል፡፡

ጥናቱን ያሰራው መቀመጫውን አምስተዳርዳም ሆላንድ ያደረገው አክሰስ ቱ ሜዲሲን የተሰኘው አለም አቀፍ መንግስታዊ ያልሆነ ተቋም ሲሆን የጥናቱን ውጤትም አሳሳቢ የህበረተሰብ ጤና ጉዳይ ነው ብሎታል፡፡