News

የትምህርት ሚኒስቴር መስሪያ ቤት የስራ ባልደረባ የነበሩ ሁለት ግለሰቦች ባልታወቁ ሰዎች በተተኮሰባቸው

ሚኒስቴሩ በማህበራዊ ትስስር ገጹ እንዳስታውቀው የመስሪያ ቤቱ  የስራ ባልደረባ የነበሩት አቶ ሙላት ጸጋዩ እና አቶ አበባው አያልነህ ለስራ ወደ አፋር ክልል በሄዱበት ነው ድንገት ባልታወቁ ሰዎች በተተኮሰባቸው ጥይት ህይወታቸውን ማጣታቸውን የገለጸው።

የሚኒስቴር መስሪያቤቱ በሁለቱ ግለሰቦች ሞት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለስራ ባልደረቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን ተመኝቷል።