InternationalNews

የእለቱ የውጭ አበይት ዜናዎች

✅የኢራን እና የአሜሪካ ተደራዳሪዎች ዛሬ በሚጀመረው  ድርድር ላይ ለመሳተፍ ፓኪስታን መዲና ኢስላም አባድ መግባታቸው ተነገረ።

✅የሊባኖስ እና የእስራኤል ተደራዳሪዎች የፊታችን ማክሰኞ በአሜሪካ መዲና ዋሽንግተን ዲሲ ድርድር እንደሚጀምሩ ቢቢሲ ዘግቧል።

✅የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አሜሪካ እና ኢራን ሊያደርጉ ያቀዱትን  ድርድር  በበጎ እንደሚቀበሉ ገልጸው፤ ሁለቱም ወገኖች በቅን ልቦና ወደ ድርድር እንዲገቡ አሳሰቡ።

✅የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚካሄደው ድርድር  ካልተሳካ ለጦርነት እየተዘጋጁ መሆናቸውን ተናገሩ።

#EBS
#EBSTVNEWS

#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews
www.ebstv.tv