EthiopiaNews

ፌዴሬሽኑ ስለ ምርጫው

የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን ባሳለፍነው ሰኞ በተካሄደው 7ኛ ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ከ32 ሺህ በላይ ወጣቶችን በታዛቢነት አሳትፎ እንደነበረ አሳውቋል።

ፌዴሬሽኑ ይህንን ያሳወቀው ትላንት በሰጠው መግለጫ ላይ ሲሆን በምርጫው በታዛቢነት ከተሳተፉ ወጣቶች መካከል ከ20 ሺህ በላይ ወንዶችና ከ12 ሺህ በላይ ሴቶች ይገኙበታል ብሏል።

በምርጫው እለት የምርጫ ጣቢያዎች ለመራጮች ምቹ እንዲሆኑ፣ አቅመ ደካሞችና ሽማግሌዎች የሚያርፉባቸው ድንኳኖችንና ወንበሮችን በማዘጋጀት ረገድም የወጣቶች ድርሻ ከፍተኛ እንደነበር ገልጿል።

የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን ጨምሮም ወጣቶች በመራጭነትም ሆነ በታዛቢነት የነበራቸው ተሳትፎ በአጠቃላይ ከፍተኛ እንደነበረም ጠቁሟል።

ፌዴሬሽኑ አክሎም ከምርጫ በኋላም በተለይ የምርጫው ውጤት ይፋ በሚሆንበት ወቅት ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ውጤቱን በጸጋ እንዲቀበሉና ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር እንዲኖር ወጣቶች የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡም ገልጿል።
ዘገባው የፍስሐ ደሳለኝ ነው።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews