EthiopiaNews

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትንበያ

የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም በፈረንጆቹ 2026 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ9.2 በመቶ እድገት እንደሚያስመዘግብ ትንበያውን ይፋ አደረገ።

የገንዘብ ድርጅቱ ይሄን ትንበያውን ይፋ ያደረገው በአሜሪካ መዲና ዋሽንግተን በመካሄድ ላይ ባለው የአይ ኤም ኤፍ እና የአለም ባንክ አመታዊ የፀደይ ጉባኤ ላይ ነው።

ድርጅቱ በፈረንጆቹ 2027 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ7.9 በመቶ እድገት ሊያስመዘግብ ይችላል ሲል ትንበያውን አስቀምጧል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በ2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ የ10.2 በመቶ እድገት ታስመዘግባለች ተብሎ እንደሚጠበቅ ከወራት በፊት መናገራቸው ይታወሳል።

መረጃው ከአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም የተገኘ ነው።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews
https://ebstv.tv/