LatestNewsPolitics

በህወሃት ታጣቂ ቡድን ከበባ ውስጥ ገብቶ ለ5 ቀናት ካለምግብና ውሀ የቆየው የሰሜን ዕዝ ጦር ከከበባ በመውጣትና ራሱን መልሶ በማደራጀት እያጠቃ ከዳንሻ ጀምሮ በርካታ ቦታዎችን መቆጣጠሩንና ወደፊትም በመገስገስ ላይ መሆኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ገልጸዋል።

ጄኔራል ብርሃኑ አክለውም በከበባ ውስጥ ገብቶ የነበረው የሰሜን እዝ ሰራዊት 4ኛ ሜካናይዝድ፣ 5ኛ ሜካናይዝድ 7ኛ ሜካናይዝድ፣ 8ኛ ሜካናይዝድ፣ 11ኛ ክፍለ ጦር፣ 20ኛ ክፍለ ጦር፣ 23ኛ ክፍለ ጦርና 31ኛ ክፍለ ጦር መሆናቸውንም ለኢዜአ ገልጸዋል።

ሰራዊቱን ከከበባ ለማላቀቅ ከምስራቅ፣ ከደቡብና ከምዕራብ ወደስፍራው በመድረስ የሰሜን እዝን ለመታደግ ለቻሉት የሰራዊቱ አመራርና አባላት የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።