News

አዲስ ነገር – የጡት ካንሰር ህክምና

በሃገራችን በርካታ ሴቶች የጡት ካንሰር ህክምና ለማግኘት ወደ ጤና ተቋማት የሚሄዱት ካንሰሩ 70 በመቶ በሰውነታቸው ውስጥ ከተሰራጨ በሁዋላ መሆኑን የፒንክ ሎተስ ኢትዮጵያ መስራች ወ/ሮ ሜሮን ከበደ ተናግረዋል፡፡

ወ/ሮ ሜሮን እንዲህ ሲሉ የተናገሩት ተቋማቸው ከሜሮን ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር በሃገራችን ያሉ የካንሰር ታማሚዎችን ለማገዝ ባዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ፕሮግራም ላይ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይ በርካታ የህክምና ሰዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።በዚህም ወቅት አሁን ላይ በሃገራችን የጡት ካንሰር እየተስፋፋ መቷል የተባለ ሲሆን በግንዛቤ እጥረት ሳቢያም በርካታ ሴቶች ህመማቸውን ተናግረው ህክምና ለማግኘት እንደሚቸገሩ ተነግሯል።

የኢቢኤስ የአዲስ ነገር / What’s New መረጃዎችን በሚከተሉት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ይከታተሉ::

ዘወትር ከሰኞ እስከ ዓርብ

👉 የማለዳ ዜና ከጠዋቱ 1:30 ሰዓት እስከ 2:00 / በድጋሚ ከ ጠዋቱ 3፡00 እስከ 3፡30

👉 የእኩለ ቀን ዜና ከቀኑ 7:30 ሰዓት እስከ 8:00 ሰዓት (በቀጥታ)

👉 የምሽት ዜና ከምሽቱ 1:30 እስከ 2:00

ዘወትር ቅዳሜ

👉 የእኩለ ቀን ዜና ከቀኑ 7:00 ሰዓት እስከ 8:00 ሰዓት

ሀገራዊ እና ዓለም አቀፍ ዜናዎች በፍጥነት እና በየእለቱ ይዘገቡበታል።

አዲስ ነገር / What’s New