EthiopiaLatestNewsSports

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ትላንት ምሽት አዲስ አበባ ገብቷል

በአፍሪካ ዋንጫ ተሳታፊ የነበረው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ትላንት ምሽት አዲስ አበባ ገብቷል በመጀመርያው ምድብ ከአዘጋጇ ሀገር ካሜሮን ጋር ተደልድሎ የነበረው ዋልያው ባደረጋቸው 3 ጨዋታዎች 1 ነጥብ ብቻ በመሰብሰብ ከውድድሩ መሰናበቱ የሚታወስ ሲሆን በትላንትናው እለት ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስም በፌዴሬሽኑ አባላትና በተለያዩ አካላት አቀባበል ተደርጎለታል። የኢትዮጵያ ከ 20 አመት በታች ሴቶች ብሄራዊ ቡድን የፊታችን እሁድ ከታንዛኒያ አቻው ጋር ጨዋታውን ያደርጋል።በኮስታሪካ አዘጋጅነት ለሚካሄደው የአለም ዋንጫ ለማለፍ 2 የደርሶ መልስ ጨዋታዎች ብቻ የሚቀራቸው እንስቶቹ በትላንትናው እለት በካፍ ልህቀት ማዕከል የሽኝት መርሃ ግብርም ተደርጎላቸዋል ቡድኑ ዛሬ ረፋድ ወደ ስፍራው ማቅናቱም ተሰምቷል:: ምንጭ :- የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 7696 ላይ ይላኩልን።Telegram: https://t.me/ebstvworldwide

Follow us on: https://linktr.ee/ebstelevision

#ኢቢኤስ #EBS