የኢትዮ_ሳዑዲ ውይይት
ኢትዮጵያና ሳዑዲ አረቢያ ስትራቴጂያዊ በሆኑ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ሊደረግ በሚችል የፋይናንስ ድጋፍ ዙሪያ መወያየታቸው ተገለጸ።
ይህ የተገለጸው በዋሽንግተን ዲሲ እየተካሄደ ካለው የዓለም ባንክና የዓለም የገንዘብ ድርጅት ስብሰባ ጎን ለጎን በተደረገ ውይይት ነው።
ውይይቱ በተለይም ለቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ሊደረግ በሚችል የፋይናንስ ድጋፍ ላይ ማተኮሩ ተገልጿል።
እንዲሁም የኢኮኖሚ ዕድገትንና ቀጣናዊ ትሥሥርን ለመደገፍ የመንገዶች ትሥሥርን ማስፋፋት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከራቸው ተጠቅሷል።
የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ ኢትዮጵያ ቅድሚያ የምትሰጣቸው የልማት ኢኒሼቲቮችን ለማሳካት ቀጣይነት ያለው ትብብር አስፈላጊ መሆኑንም አንስተዋል።
የሳዑዲ የልማት ፈንድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሱልጣን አብዱልራህማን በበኩላቸው የሀገሪቱን ዋና ዋና የልማት ተነሳሽነቶች ለመደገፍ ትብብራቸውን ለማጠናከር ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews
https://ebstv.tv/
