የእስራኤል ጥቃት በሊባኖስ
🔸እስራኤል ትላንት በደቡብ ሊባኖስ በፈፀመችው ጥቃት በትንሹ 13 የአካባቢው ነዋሪዎች ተገደሉ።
🔸ከትላንቱ ጥቃት ከአንድ ቀን በፊት እስራኤል በናቤቴ ከተማ በፈፀመችው ጥቃት የተጐዱ ነዋሪዎችን ነፍስ ለማዳን የተሰማሩ እርዳታ ሰራተኞችም ተገድለዋል።
🔸የቤይሩት መንግስት በቅርቡ የተኩስ አቁም ከተደረገ በኋላ 380 ዜጐቿ በተጠናከረው የእስራኤል የአየር ድብደባ መገደላቸውን ይገልፃል።
🔸በአካባቢው የሚንቀሳቀሰው የሄዝቦላ መሪ ናይም ቃስም በፊናቸው ድርጅታቸው ጦርነቱ እስራኤልን ወደሚለበልብ የምድር ገሀነም እንቀይረዋለን እያሉ ነው።
🔸እስራኤል ዛሬ በፈፀመችው ጥቃትም ከቤይሩት ወደ ደቡባዊ ሊባኖስ በሚያመራ አውራ ጐዳና ላይ የነበረ ተሽከርካሪን በሚሳኤል መታለች።
🔸ኤፍፒ እንደሚለው እስራኤል ጥቃቱን እንዲህ ያፋፋመችው ከቤይሩት ጋር የደረሰችው ተኩስ አቁም ባለበት ሁኔታ ነው።
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews
