EthiopiaLatestNewsOthers

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለይፋዊ ስራ ጉብኝት ኬንያ ሞያሌ ገብተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ሞያሌ ሲደርሱ የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

                                                                                                                                                                                                                                                            

መሪዎቹ የሐዋሳ-ቡሌ ሆራ-ያቤሎ-ሜጋ-ሞያሌ መንገድና የጋራ ፍተሻ ጣቢያ ፕሮጀክትን መርቀው ከፍተዋል።

500 ኪ.ሜ ርዝመት ያለውና የሞምባሳ-ናይሮቢ-አዲስ አበባ ኮሪደር አካል የሆነው መንገዱ ኢትዮጵያን ከኬንያ የሚያስተሳስር መሆኑ ተገልጿል።

የሐዋሳ-ቡሌ ሆራ-ያቤሎ-ሜጋ-ሞያሌ የአስፓልት ኮንክሪት መንገድ 6 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ወጪ እንደተደረገበት ተገልጿል። ዘገባው የኢቢሲ ነው።#አዲስ_ነገር #Whatsnew_ebs