EthiopiaNews

ትምህርት ሚኒስቴር በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የ9ኛና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ምዝገባ መጀመሩን አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ መስፈርቱን የሚያሟሉ የ9ኛና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን እስከ ነሃሴ 15 2018 አ.ም ድረስ መመዝገብ እንደሚችሉ ገልጿል ።

መስፈርቱን የሚያሟሉ ተማሪዎች ምዝገባቸውን ባሉት ሆነው ሚነስቴሩ ባዘጋጀው የመመዝገቢያ ፖርታል በኦንላይን መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።

ሚኒስቴሩ ለፈተና የሚቀርቡ ተማሪዎች ዝርዝር እና የፈተና ጊዜ ወደፊት የሚገለፅ ይሆናል በሏል።

የመመልመያ መስፈርቱን አሟልተው የሚያልፉ ተማሪዎች በተመደቡበት ልዩ አዳሪ ት/ቤት ለመማር ፈቃደኛ መሆን እንዳለባቸው ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካች ተማሪዎች በዚህ ሊንክ https://sbs.moe.gov.et/apply መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን ተገልጿል።