የአሜሪካው ቦይንግ ኩባንያ አፍሪካ በሚቀጥሉት 20 ዓመታት ውስጥ የሚስፈልጓትን 75 ሺህ አዳዲስ የአቪዬሽን ባለሙያዎችን ለማብቃት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ገለጸ፡፡
ኩባንያው ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው አራተኛው የስልጠና መርሃ-ግብር ላይ 28 የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በአቪዬሽን ሙያ ለመሰማራት የሚያስችላቸውን የስድስት ሳምንታት ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ መቻሉንም ነው የገለጸው፡፡
ስልጠናው የዲጂታል ክህሎቶችን እና የተግባር ልምምዶችን ያካተተ መሆኑን የገለጸው ኩባንያው በዚሁ መርሃ ግብር ባለፉት ጥቂት አመታት ከ100 በላይ የኢትዮጵያ ተማሪዎችን ማብቃት መቻሉንም ገልጿል፡፡
