InternationalNews

የደቡብ ኮሪያው ፕሬዝዳንት ሊ ጄ ምዩንግ ሀገራቸው በሆርሙዝ ባህር አካባቢ በሚካሄዱ ማናቸውም ቀጥታ ጦርነቶች ውስጥ የሚሳተፉ ተዋጊ ወታደሮችን እንደማትልክ በይፋ አስታውቀዋል።

ፕሬዚዳንቱ በሰጡት መግለጫ ሀገራቸው በውጭ ሀገራት ግጭት ውስጥ ላለመግባት ያላትን ጽኑ አቋም እንደምትጠብቅ ገልጸው፣ ሆኖም የዜጎቿን ደህንነት፣ የንግድ መርከቦቿን እና የነዳጅ ማጓጓዣ መስመሮቿን ለመጠበቅ ወሳኝ የመከላከያ እርምጃዎችን እንደምትወስድ አረጋግጠዋል።

ይህ ውሳኔ የተላለፈው አሜሪካ በቀጠናው የባህር ላይ ስጋቶችን ለመግታት ከሴኡል ወታደራዊ ድጋፍ እንድታደርግ ጫና በምታደርግበት ወቅት ሲሆን፣ ደቡብ ኮሪያም የነዳጅ አቅርቦቷን ለማረጋገጥ የሚረዱ ህጋዊ እና አነስተኛ የመከላከያ አማራጮችን በማስላት ላይ እንደምትገኝ ተመልክቷል።