EthiopiaNews

የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 2ሺህ 212 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን አስታወቀ፡፡

‎በሳምንቱ ውስጥ በተደረገ 10 ዙር በረራ የተመለሱት 2ሺህ 210 ወንዶችና 1 ሴት እንዲሁም 1 ጨቅላ ህፃን ሲሆን ከተመላሾች መካከል 38 እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሚገኙበት ሚኒስቴሩ ገልጿል።

‎ሚኒስቴሩ መስከረም 5/ 2018 አ.ም በተጀመረው ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ እስካሁን ከ94 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር መመለስ ተችሏል።

‎ሚኒስቴሩ ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የማድረግ እና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ስራ ከሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር በመተባበር እየሰራሁ ነው ብሏል።