የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ከአያት 49 ወደ ፊጋ በሚወስደው መንገድ ላይ 72 ድልድይ አካባቢ ከዛሬ ሰኞ ጀምሮ መንገዱ በከፊል ለትራፊክ ዝግ እንደሚደረግ አስታውቋል።
መንገዱ በከፊል ለትራፊክ ዝግ የሚሆነው የመንገድ ጥገና ሥራ ለማካሄድ መሆኑን ባለስልጣን መ/ቤቱ ገልጿል።
ስለሆነም አሸከርካሪዎች ጥንቃቄ በማድረግ እንዲተላለፉ እና አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ አሳስቧል።መረጃው ከአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን የተገኘ ነው።
