የፈሳሽ ትራንስፖተሮች ከጥቅምት 30 በኋላ ሥራ እንደሚያቆሙ አስታወቁ
የፈሳሽ ትራንስፖርተሮች መንግሥት ተገቢውን የተመን ዋጋ ማስተካከያ ካላደረገ ከጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም. በኋላ ሥራ እንደሚያቆሙ አስታወቁ፡፡
ማኅበሩ ዛሬ ጥቅምት 17 ቀን 2013 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ አባላቱ የሚገጥማቸውን ችግሮች ጠቅሶ፣ ለመንግሥት መፍትሔ ይሆናል ያለውን ሐሳብ ቢያቀርብም ከመንግሥት ወገን ተገቢውን ምላሽ ባለማግኘቱ ከጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም. በኋላ ሥራ ለማቆም እንሚገደዱ በአንድ ድምፅ መወሰናቸውን አስታውቋል፡፡ የዚህ ውሳኔያቸው መነሻ በማኅበሩና ሌሎች አካላት ተጠንቶ የቀረበ መፍትሔ ሐሳብን ወደ ጎን በመተው፣ መንግሥት ያደረገው የታሪፍ ማስተካከያ በዘርፉ ለሚታየው ችግር ምንም ዓይነት ተጨባጭ መፍትሔ ሊሰጥ ባለመቻሉ ምክንያት እንደሆነ የማኅበሩ ቦርድ አባላት ገልጸዋል፡፡