EthiopiaNews

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2019 በጀት ዓመት የ10 ነጥብ 1 በመቶ እድገት ያስመዘግባል ተብሎ እንደሚጠበቅ የገንዘብ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

በሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት 25ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው የፌዴራል መንግስት የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት መግለጫን ያቀረቡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ በተያዘው በጀት ዓመት ከመካከለኛው ምስራቅ ግጭት የመነጩ ጫናዎችን በመቋቋም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ10 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት እንደሚመዘገብ መገመቱን ጠቅሰዋል፡፡

ከ2012 እስከ 2016 ባሉት ዓመታት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በአማካይ በየዓመቱ የ6 ነጥብ 8 በመቶ እንዲሁም በ2017 የ9 ነጥብ 2 በመቶ እድገት መመዝገቡን ያነሱት ሚኒስትሩ በቀጣዩ በጀት አመት ደግሞ የ10 ነጥብ 1 በመቶ እድገት ይመዘገባል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተናግረዋል፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews