EthiopiaNews

ባለፉት 9 ወራት በዲጅታል አማራጭ የተደረገ የግብይት መጠን 24.2 ትሪሊዮን ብር መድረሱ ተነገረ።

የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ ባለፉት 9 ወራት በዲጅታል አማራጭ የተደረገ የግብይት መጠን 24.2 ትሪሊዮን ብር መድረሱን ተናገሩ።

ገዥው ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ይሄን ያሉት ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር በሚል መሪ ቃል ትናንት በተካሄደ የ“ኢትዮጵያ ታከናውናለች” ጉባኤ ላይ ነው።

ገዥው ባለፉት 9 ወራት በሞባይል የተደረገ የገንዘብ ልውውጥ 2.9 ትሪሊየን ብር መድረሱን በመድረኩ ገልፀዋል።

ኢዮብ ተካልኝ ባለፉት 8 አመታት የባንኮች አጠቃላይ ሃብት ወደ 6.38 ትሪሊየን ማደጉን እንዲሁም እና የባንኮች የተቀማጭ ገንዘብ ደግሞ 4.5 ትሪሊዮን ብር መግባቱን ተናግረዋል።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews