EthiopiaNews

ሰራተኞች ስራን ለማቅለል የተቋማትን ምስጢራዊ መረጃዎች ወደ መተግበሪያዎቹ የሚጫኑበት መጠን መጨመሩ ተነገረ።

ሰራተኞች ስራቸውን በፍጥነት ለማከናወን በማሰብ የተቋማትን ምስጢራዊ መረጃዎች ወደ ሰው ሰራሽ አስተውሎት መተግበሪያዎች የሚጭኑበት መጠን ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ ብቻ በ93 በመቶ መጨመሩን አንድ አዲስ ጥናት ማመላከቱን የኢነፎርሜሽን መረብ ደህንነት ገለጸ፡፡

ይህ ድርጊት ተቋማትን ለመረጃ መንታፊዎች በማጋለጥ ለመረጃ ብዝበዛ እንደሚዳርግ የተነገረ ሲሆን ሰራተኞች በስፋት ከሚጠቀሙባቸው ውስጥ ግራመርሊ38 በመቶ እንዲሁም ቻትጂፒቲ ደግሞ 21 በመቶ ድርሻ እንደሚወስዱ ጠቁሟል፡፡

ሰራተኞች ወደ መተግበሪያዎቹ ከላኳቸው ምስጢራዊ መረጃዎች መካከል የተቋማት የፋይናንስ ሰነዶች፣ የግለሰቦች የግል መረጃዎች እና የኮምፒውተር ሶፍትዌር ኮዶች እንደሚገኙበት ተነግሯል።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews