EthiopiaLatestNews

በሴቶች ጥቃት እና ሰላም አምጪነት ዙሪያ ዉይይት ተደረገ

የሰላም ሚኒስቴር ከአይ ኤስ ኤስ/Institute for Security Studies/ ጋር በመተባበር የሴቶችን ጥቃት እና የሰላም አስተዋጾ ላይ ተወያዩ፡፡

በሚኒስቴር መ/ቤቱ የብሔራዊ መግባባትና ማኅበራዊ ሃብት ግንባታ ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሚናስ ፍስሓ በፓለቲካ አለመግባባት ምክንያት በሚፈጠሩ ግጭቶች ሴቶች የመጀመሪያው ተጠቂ እንደሚሆኑ ገለጸዋል። ግጭቶችን ለመፍታትና ሰላምን ለማጎልበት ሴቶች ከፍተኛ አስተዋጾ እንዳላቸዉም ተናግረዋል፡፡

በመድረኩ ኢትዮጵያ በገጠማት ችግር የሴቶች ጥቃት እንዲሁም በሰላም ግንባታ እረገድ ሚያደርጉትን ከፍተኛ ጥረት አስመልክቶ ሰፊ ምክክር ተደርጓል።