News

አዲስ ነገር – ዓመታዊ የጤና ጉባኤ

ባለፈው የ2014 በጀት ዓመት በ49 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ወጪ የተለያዩ የመድኃኒት፣ ክትባትና የህክምና መገልገያ እቃዎች ወደ ሀገር ማስገባቱን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።ሚኒስቴሩ ይህንን ያስታወቀው 24ኛው ዓመታዊ የጤና ጉባኤውን በሐዋሳ ከተማ እያካሄደ ባለበት ወቅት ነው።በጉባኤው ላይ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በ2014 በጀት አመት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትና ያጋጠሙ ችግሮችን እንዲሁም የ2015 በጀት ዓመት እቅዶችን ያቀረቡ ሲሆን በተለያዩ የጤና ዘርፎች የላቀ አስተዋጽኦ ያበረከቱት የጤና ባለሙያዎችም ከሲዳማ ክልል ፕሬዝዳንት ደስታ ሌዳሞ እጅ እውቅናና ሽልማት ተቀብለዋል።

የኢቢኤስ የአዲስ ነገር / What’s New መረጃዎችን በሚከተሉት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ይከታተሉ::

ዘወትር ከሰኞ እስከ ዓርብ

👉 የማለዳ ዜና ከጠዋቱ 1:30 ሰዓት እስከ 2:00 / በድጋሚ ከ ጠዋቱ 3፡00 እስከ 3፡30

👉 የእኩለ ቀን ዜና ከቀኑ 7:30 ሰዓት እስከ 8:00 ሰዓት (በቀጥታ)

👉 የምሽት ዜና ከምሽቱ 1:30 እስከ 2:00

ዘወትር ቅዳሜ

👉 የእኩለ ቀን ዜና ከቀኑ 7:00 ሰዓት እስከ 8:00 ሰዓት

ሀገራዊ እና ዓለም አቀፍ ዜናዎች በፍጥነት እና በየእለቱ ይዘገቡበታል።

አዲስ ነገር / What’s New