የአሜሪካ የጨረቃ ጉዞ
አሜሪካ ከሃምሳ ዓመታት በኋላ ሰው የጫነች መንኮራኩርን ወደ ጨረቃ ላከች።
አርቴሚስ ሁለተኛ የተባለ ስያሜ የተሰጣት መንኮራኩር አራት ጠፈርተኞችን የያዘች ሲሆን በአሁኑ ወቅት በመሬት ምህዋር ዙሪያ እየተሽከረከረች ትገኛለች ተብሏል።
አርሜቲስ ሁለተኛ መንኮራኩር ለ24 ሰዓታት በምድር ምህዋር ከተሽከረከረች በኋላ ሁሉ ነገር የተሳካ ከሆነ ወደ ጨረቃ በረራዋን ትጀምራለች።
የአሜሪካ የጠፈር ምርምር ባለስልጣናት እንደሚሉት የአሁኖቹ ጠፈርተኞች በአስር ቀን ጉዟቸው ጨረቃ ላይ ሳያርፉ እንዲሁ ዞረዋት ይመለሳሉ ይሁንና የሰው ልጅ እስካሁን ከሄደበት ርቀት በላይ ይጓዛሉ ተብሏል።
ጠፈርተኞቹ ከ50 ዓመታት በፊት እንደተደረገው የጨረቃ ጉዞ ለምን ጨረቃ ላይ እንደሚያርፉ የተገለፀ ነገር የለም።ሕንድ ከጥቂት ዓመታት በፊት ከጨረቃ ጀርባ መንኮራኩር ማንሳፈፏ አነጋጋሪ ሆኖ ነበር።
#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews
