EthiopiaNews

የዕጩ ወኪሎች ግዴታ

ማንኛውም ተዘዋዋሪም ሆነ ተቀማጭ የዕጩ ወኪሎች ግዴታ ምን ምን ናቸው?

👉የምርጫ ኃላፊው የሚሰጠውን ትዕዛዞች ማክበር አለበት፣

👉የምርጫ ሂደቱን ከሚያውኩ ተግባራት መቆጠብ አለበት፣

👉አግባብ ባለው አካል ሲጠየቅ መታወቂያውን ማሳየት አለበት፣

👉የምርጫ ሕጉን ማክበር አለበት፣

👉የምርጫውን ሂደት የመከታተል ተግባሩን ሲያከናውን መራጮች ማንን መምረጥ እንዳለባቸው አስተያየት ከመስጠት ወይም ተጽዕኖ ለማሳደር መሞከር የለበትም፣

👉የምርጫ ቁሳቁሶችን መያዝ፥ ማንሳት፤ መነካካት ወይም በቁሳቁሶቹ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ተግባራትን መፈጸም የለበትም፣

👉የምርጫ ጣቢያውን ኃላፊ ወይም ሠራተኛ ከማስፈራራት ወይም ሥራውን ከሚያደናቅፉ ተግባራት መቆጠብ አለበት፣

👉ወደ ድምፅ መስጫ ክፍሎች መግባት የለበትም፣

👉ቦርዱ የሚያወጣውን የሥነ ምግባር ደንብ መፈረም እና ማክበር ይገባዋል፡፡

መረጃው ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተገኘ ነው።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews
www.ebstv.tv