የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀነራል ብርሀኑ ጁላ ከተናገሩት የተወሰደ።
ህወሀት ቡድን በመደምሰሱ ምክንያት መደበኛው ጦርነት ተጠናቋል። አሁን በየስራ ስሩ ያሉትን ወንጀለኞችን ፈልጎ የማውጣት ተልዕኮ ብቻ ነው የሚፈጸመው።
- በዚህ ድል በዋናነት ሊደሰት የሚገባው የትግራይ ህዝብ ነው። ህዝቡ በአሁኑ ሰዓት ወንጆለኞቹን አስራችሁ የተቋረጡ የስልክ የመብራት አገልግሎቶች ተጀምረው እንደ በፊቱ ህዝቡ በሰላም እንዲወጣ እንዲገባ እየጠየቀ ነው ብለዋል።
- አሁን ባለው ሂደት ወንጀለኞቹ ከያሉበት በማውጣት ለህግ ማቅረብ ዋነኛ ስራው ነው ያሉት ጀነራሉ ህዝቡም የወንጀለኛ ቡድኑን እንዲያጋልጥ ለቅሞ እንዲያስረክብ ጥሪ አቅርበዋል።
- ከዚህ በኃላ ከተማ ተቆጣጠርን ሳይሆን እከሌ የተባለ ወንጀለኛ በቁጥጥር ስር ዋለ የሚሉ ዜናዎችን ነው ለህዝባችንና ለሚዲያው የምንገልጸው ብለዋል:: የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀነራል ብርሀኑ ጁላ ከሰዓታት በፊት በሰጡት መግለጫ።#አዲስ_ነገር #Whatsnew_ebs
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በቴሌግራም https://t.me/ebstvworldwidebot ይላኩልን::
Subscribe to EBS on YouTube: https://bit.ly/2M1aRZL
Follow EBS on Telegram: https://t.me/ebstvworldwide
Follow EBS on Facebook: https://bit.ly/2s439TS