ቢቢሲ እንደዘገበው የፕሬዝዳንቱ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ፈርመውበታል በተባለ ሀሰተኛ ደብዳቤ በግዙፉ የፕሬዝዳንቱ ህንጻ ውስጥ የባህር ማዶ እንቅስቃሴ ማበልጸጊያ የተባለ የሀሰት መስሪያ ቤት ቢሮ እንዲሰጠውና የመንግስት 1 ሚሊዮን ዶላር ወጪ እንዲደረግለት ሆኗል።
ፖሊስ ጉዳዩን ከደረሰበት በኋላ ሀሰተኛውን ደብዳቤ ያዘጋጀውና የጽህፈት ቤቱ ዳይሬክተር ነኝ የሚል አንድ ግለሰብ ከመኖሪያው መሰወሩ ተገልጿል።
ጽህፈት ቤቱን እስከመፈጠሩ የማያውቁት የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ቦላ ቲኒቡ የሀገሪቱ የጸር ሙስና ኮሚሽን ጉዳዩን እንዲያጣራ ትእዛዝ ሰጥተዋል።
