የፌደራል ፖሊስ አክሎም በቁጥጥር ስር የዋሉ የሰዎች አዘዋዋሪዎች የምርመራ መዝገብም በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማደራጀት ለፍትሕ ሚኒስቴር መላኩንም አስታውቋል።
ተጠርጣሪዎቹ ሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር መረብ በመዘርጋት፣ተጎጂዎቹ በየመን በኩል ወደ ሳውዲ አረቢያ ገብተው የተሻለ ኑሮ እንደሚኖሩ በደላሎች አማካኝነት በመመልመል ሲልኩ መቆየታቸውንም ፖሊስ ገልጿል።
ተጎጂዎችም ከኢትዮጵያ ድንበር በማሻገር በየመን ሀገር ውስጥ በሚገኙና ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጁ መጋዘኖች ታጉረው ከፍተኛ ኢሰብአዊ ድርጊቶች ይፈጸሙባቸው ነበር ብሏል።
እነዚሁም ሀገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ከ1 ቢሊየን ብር በላይ ገንዘብ በመቀበል ከ40 ሺህ በላይ ሰዎችን ማዘዋወራቸውን የገለጸው ፖሊስ ከ60 ሰዎች በላይ ለሕልፈተ መዳረጋቸው እንዲሁም በርካታ ሴቶች መደፈራቸውን በምርመራ ደርሸበታል ሲል ዛሬ ይፋ ባደረገው መግለጫው አስታውቋል።
በዚህ ጉዳይ በርካታ ሰዎች የምስክርነት ቃላቸውን የሰጡ መሆኑንና በተለይ ከሳውዲ አረቢያና ከኢትዮጵያ በቀጥታ መስመር የቪዲዮ የምስክርነት ቃላቸውን መስጠታቸውን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ መረጃ ያሳያል
