InternationalNews

ትራምፕ በኤየር ፎርስ ዋን ፕሬዝዳንታዊ አውሮፕላኖች ላይ ሆነው ለጋዜጠኞቸ በሰጡት ቃለ መጠይቅ ኢራን የደረሰባቸውን ከባድ ጥቃት አሁን የሚረዱት ይመስለኛል ያሉ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት መካከል የሚደረገው ድርድርም ዳግም ይጀመራል ብለዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ በኢራን ላይ ሲፈጽሙ የቆዩትን ጥቃትም ያቆሙት በቀጠናው በሚገኙ የአሜሪካ ወዳጅ ሀገራት ጥያቄ እና ከኢራን ከራሷ በመጣ ጥያቄ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ከኢራን ጋር በሚደረገው ድርድር በምን ያህል ጊዜ ውስጥ ከስምምነት ላይ እደርሳለሁ ብለው እንደሚያስቡ የተጠየቁት ትራምፕ ሰዎችን የመግደል ሱስ የለብኝም ያሉ ሲሆን ድርድሩ በምን ያህል ጊዜ ውጤት እንደሚያመጣ በጋራ እንመለከታለን ብለዋል፡፡