EthiopiaNews

ኢትዮጵያ ከቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የምታስተናግደው ጉባዔ ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገልጿል።

በጉባዔው ከ47 የአፍሪካ አባል ሀገራት የተወጣጡ የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች እና ለጋሾችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች እንደሚሳተፉ ታውቋል።

ለ5 ቀናት በሚዘልቀው ጉባኤው በአፍሪካ የጤና ተደራሽነት ለማስፋት በሚያስችሉ ስትራቴጂዎች ላይ ይስማማሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል።