EthiopiaNews

የአየር መንገዱ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ይሄን ያሉት ዛሬ የተቋሙን አፈጻጸም በተመለከተ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።

ዋና ስራ አስፈጻሚው ገቢው ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ20 በመቶ ብልጫ እንዳለውና በ2018 በጀት ዓመት ከተያዘው ዕቅድ ጋር ሲነጻጸር ደግሞ የ9 በመቶ ብልጫ አለው ነው ያሉት።

ዋና ስራ አስፈጻሚው በበጀት ዓመቱ አራት አዳዲስ ዓለም አቀፍ የበረራ መዳረሻዎች መከፈታቸውን እንዲሁም አየር መንገዱ 20 ነጥብ 7 ሚሊዮን መንገደኞችን ማጓጓዙን ተናግረዋል።