የሲቪል ማህበራት ቀጣዩ እና የበለጠው ወሳኝ ተግባር የሃገራዊ ምክክሩ ምክረ ሃሳቦችን ወደ ተጨባጭ እርምጃ መቀየር መሆኑን የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ም/ቤት አስታወቀ።
ም/ቤት ይሄን ያለው የሃገራዊ ምክክሩ መጠናቀቅን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ነው።
ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሃገራዊ ምክክሩ ወቅት በአመካካሪነት ፣በተሳታፊነት ፣ በአማካሪነት እና በታዛቢነት ሚናዎች ላይ በመሳተፍ ገንቢ ሚና መጫወታቸውን ም/ቤቱ አስታውሷል።
ም/ቤቱ ሃገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያውያን የመነጋገር ፣ የመደማመጥ እና ያላግቧቧቸውን ጉዳዮች ሁሉንም ተጠቃሚ ባደረገ መንገድ የመፍታት አቅም እንዳላቸው ያሳየ ነው ብሏል።
የሲቪል ማህበራት ቀጣዩ እና ወሳኝ ተግባር የምክክሩ ምክረ ሃሳቦችን ወደ ተጨባጭ እርምጃ መቀየር ፣የሕዝብ ተሳትፎ ማስቀጠል ፣መተማመንን ማጠናከር እና ልዩነቶችን በግጭት ሳይሆን በውይይይት የሚፈቱበትን ባሕል ማሳደግ መሆኑን ም/ቤቱ ገልጿል።
ም/ቤቱ የምክክር ባሕል ማስቀጠል እ የምክክሩን ውጤት ወደ ሰላማዊ አካታች እና ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ግንባታ መቀየር ይኖርብናል ብሏል።መረጃው ከኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ም/ቤት የተገኘ ነው።
