InternationalNews

አሜሪካ ከኢራን ጋር በተደረሰው ስምምነት መሰረት በሆርሙዝ ሰርጥ የሚተላለፉ መርከቦች ከኮቴ ክፍያ ነፃ እንደሚሆኑ አሳወቀች።

የዋሽንግተን ባለስልጣናት ኢራን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞችን ማግኘት ከፈለገች መሰሉን ግዴታዋን ማሟላት አለባት ያሉ ሲሆን ለኢራን መልሶ ግንባታ አሜሪካ የምትለቀው 300 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍም በስምምነቱ አፈጻጸም ላይ ይመሰረታል ብለዋል፡፡

ባሳለፍነው እሁድ ከአሜሪካ በኩል ፕሬዝዳንት ትራምፕና ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ እንዲሁም ከኢራን በኩል የሀገሪቱ የፓርላማ አፈ ጉባኤ ሆነው በዚህ የመግባቢያ ስምምነት ላይ በበይነ መረብ መፈራረማቸውም ተሰምቷል፡፡

የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ጂዲ ቫንስ ለሲ.ኤን.ኤን ቴሌቪዥን ጣብያ በሰጡት ማብራሪያ ደግሞ የፊታችን አርብ በስዊዘርላንድ ሁለቱ ሀገራት ፊት ለፊት ተገናኝተው የሚፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት አንድ ገፅ ከግማሽ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews