ባህርዳር ዩንቨርስቲ የክብር እና የአድናቆት ሽልማት አገኘ
የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት በ10ኛው ዙር አገር አቀፍ የጥራት ሽልማት መርሀግብሩ 38 ድርጅቶችና ተቋማትን ተሸላሚ አድርጓል።
በዚህ ሽልማት መርሀግብር የባህር ዳር ዩንቨርስቲ የዘንድሮ የክብር ና የአድናቆት ተሸላሚ አድርጎታል ::
የኢፌዴሪ ርዕሰብሔር ና የድርጅቱ የበላይ ጠባቂ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት በብሔራዊ ቤተ-መንግስት በተካሄደው ስነስርዓት ነው ይህ የተገለፀው ::