ዩክሬን በሩሲያዋ ኖቮርሲክ ወደብ ላይ በፈፀመችው ግዙፍ የድሮንና የሚሳኤል ጥቃት ሁለት የሩሲያ ታላላቅ የእህል መጫኛ ተርሚናሎች ተመቱ።
ቢቢሲ የጠቀሰው ሪፖርት እንደሚለው ይሄ ጥቃት በጥቁር ባህር በሚገኝ አንድ የባህር ኃይል መደብ ላይም ደርሷል።
በጥቃቱም አንድ የስምንት ዓመት ልጅን ጨምሮ ሦስት ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት ተናግረዋል።
የዩክሬኑመሪ ቮሎድሚር ዜሌንስኪ አገራቸው በሮኬት፣ በጦር ጄትና በሰው አልባ ድሮን ጀልባዎች ጥቃቱ በጥንቃቄ መፈፀሙን ገልፀዋል።
ዜሌንስኪ ተመቱ ስለተባሉት ሁለት የእህል መጫኛ ተርሚናሎች ያሉት ነገር የለም።
የዩክሬን ጦር በፊናው ሁለት ፈጣን የውጊያ መርከቦችን ጨምሮ አራት መርከቦች ተመተዋል ሲል መግለጫ አውጥቷል።
